on | 2025-11-18 13:17:17
Share: Facebook | Twitter | Whatsapp | Linkedin
ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የ3ኛ ዓመት ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁ
ለአንድ ዓመት የማስተማር አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድደው
መመሪያ በ2019 የትምህርት ዘመን ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።
ለመምህራን የሚቀርበው ጥቅማጥቅምና ደመወዝ በቂ አለመሆን
ለመምህራን እጥረት ምክንያት እንደሆነ የትምህርት ሚኒስትሩ
ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ለምክር ቤት አባላት ተናግረዋል። ይህም አዲስ
መምህራንን በበቂ ሁኔታ ለማፍራት አስቸጋሪ እንዳረገው
ገልፀዋል።
የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ግለሰቦች የአንድ ዓመት የማስተማር
ዘዴ (Pedagogy) ኮርስ በመውሰድ ለመምህርነት ብቁ መሆን
እንደሚችሉ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። በዚህም የመምህራንን ቁጥር
ለማሳደግ ይቻላል ብለዋል።
የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለአንድ ዓመት የማስተማር አገልግሎት
ሲሰጡ፣ የበለጠ የመምህነነት ሙያ ፍቅር ሊያጎለብቱ
እንደሚችሉም ገልፀዋል።
ባለፈው ዓመት ከቅድመ-አንደኛ እስከ 12ኛ ክፍል በሀገሪቱ
አጠቃላይ የመምህራን ቁጥር 625,000 የነበረ ሲሆን፤ በዚህ ዓመት
ቁጥሩን ወደ 700,000 ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑ ተገልጿል።
በወላይታ ብሔር ዘንድ ልዩ ቦታ የሚሰጠው "ጊፋታ”
በቶኪዮ የወርቅ መርገም አልሰበር ያላት ኢትዮጲያ