ከይር ቮክስ አፍሪካ

ዜና አለም አቀፍ

ቱርክ የታጋቾች አስከሬኖች ፍለጋን የሚያግዙ 81 የእርዳታ ሰራተኞች ወደ ጋዛ ላከች

on | 2025-10-17 12:28:49

Share: Facebook | Twitter | Whatsapp | Linkedin


ቱርክ የታጋቾች አስከሬኖች ፍለጋን የሚያግዙ 81 የእርዳታ ሰራተኞች ወደ ጋዛ ላከች

ጋዛ ዉስጥ እንደታገቱ የሞቱ የእስራኤል የታጋቾች አስከሬኖች ፍለጋን የሚያግዙ 81 የአደጋ ጊዜ እርዳታ ሰራተኞች ወደ ጋዛ መላኳን ቱርክ አስታወቀች።

የቱርክን መከላከያ ሚኒስቴርን ምንጭ ጠቅሶ AFP እንደዘገበው ባለሞያዎቹ እገዛ የሚያደርጉት እስካሁን ያልተገኘ የ19 ታጋቾችን አስከሬን ፍለጋን ነው።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዳለው የሰዎቹ ተልዕኮ ሰብዓዊ እርዳታ ማስተላለፍ፣ አስከሬኖችን መፈለግ እና የተኩስ አቁሙን ማስጠበቅ ነው።

የቱርክ የአደጋ ጊዜ እርዳታ ሠራተኞች ከቱርክ በተጨማሪ ሶማሊያ የፍልስጤም ግዛቶች ኢኳዶርና በፊሊፒንስ ጨምሮ ከ50 በሚበልጡ ሀገራት  የሕይወት አድንና የሰብአዊ እርዳታ ተልዕኮዎችን አከናውነዋል።

ፈልግ

አስተያየትዎን ይተው