ከይር ቮክስ አፍሪካ

ዜና አለም አቀፍ

ትራምፕ የጋዛ ሰላም ንግግር በአፋጣኝ እንዲጀምር ለአደራዳሪዎች ጥሪ አቀረቡ

on | 2025-10-06 19:19:08 on2025-12-01 00:51:41

Share: Facebook | Twitter | Whatsapp | Linkedin


ትራምፕ የጋዛ ሰላም ንግግር በአፋጣኝ እንዲጀምር ለአደራዳሪዎች ጥሪ አቀረቡ

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የጋዛን ጦርነት ማስቆም ጥረት ላይ እየተሳተፉ ያሉ ሁሉም በእስራኤል እና በሐማስ መካከል በግብፅ የሚደረገውን ቀጥተኛ ያልሆነ ንግግር እንዲያፋጥኑ ጥሪ አቅርበዋል።

ንግግሩ ሐማስ ታጋቾችን መልቀቅ እና የጋዛን አስተዳደር ለምሑራን (ቴክኖክራት) መስጠትን ጨምሮ በትራምፕ ባለ 20 ነጥብ የሰላም ስምምነት ዕቅድ ላይ ከተስማማ በኋላ የሚደረግ ሲሆን፤ ቡድኑ በሌሎችም ጉዳዮች ላይም የመነጋገር ፍላጎት አለው።

ትጥቅ መፍታት እና በመጪው የጋዛ መንግሥት ላይ ምንም ተሳትፎ እንደማይኖረው የሰላም ዕቅዱ ቁልፍ ክፍል ላይ ቡድኑ ምላሽ አልሰጠም።

በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ንግግሩ "በጣም ውጤታማ" ነበር ያሉት ትራምፕ፤ "የመጀመሪያው ምዕራፍ በዚህ ሳምንት እንደሚጠናቀቅ ተነግሮኛል። እና ሁሉንም የምጠይቀው እንዲያፋጥኑት ነው" ብለዋል።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት አክለውም፤ "ጊዜው በጣም አንገብጋቢ ነው ወይም ደም መፋሰስ ይቀጥላል" ብለዋል።


ፈልግ

አስተያየትዎን ይተው