on | 2025-10-04 06:44:36 on2025-12-01 00:52:01
Share: Facebook | Twitter | Whatsapp | Linkedin
6ኛው የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤትና የፌዴሬሽን ም/ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን መክፈቻ ሥነ ሥርዓት ሰኞ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የአንድ ዓመት የሥራ ጊዜ ከመስከረም ወር የመጨረሻ ሳምንት ሰኞ እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ መሆኑ ተደንግጓል፡፡
በዚህ መሰረትም የ6ኛው ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የተጠናቀቀ ሲሆን ÷ 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ ሥርዓትም ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተገኙበት በመጪው ሰኞ ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል፡፡
ፕሬዚዳንት ታዬ ለሁለቱ ምክር ቤቶች ዓመታዊ ሥራቸውን እንደጀመሩ በማብሰር የፌደራል መንግስቱን ዓመታዊ ዕቅድ የሚያቀርቡ ይሆናል፡፡
በወላይታ ብሔር ዘንድ ልዩ ቦታ የሚሰጠው "ጊፋታ”
በቶኪዮ የወርቅ መርገም አልሰበር ያላት ኢትዮጲያ